=<({አል-ኢኽላስ 112:1-4})>=
ﺑﺴﻢ ﺍﻟﻠﻪ ﺍﻟﺮﺣﻤﻦ ﺍﻟﺮﺣﻴﻢ
1. በል! እርሱ አላህ አንድ ነው።
2. አላህ (የሁሉ) መጠጊያ ነው።
3. አልወለደም፤ አልተወለደምም።
4. ለእርሱም አንድም ብጤ የለውም።
![]() =<({አል-ቁርአን 96:1-5})>=
![]() በቡኻሪ በተዘገበው ሐዲስ መሰረት እውቀትን መሻት በእያንዳንዱ ሙስሊም ላይ ግዴታ ነው። ![]() |
---|
ከክፉ የራቀ
ለኸይር የታጠቀ
ለአኺራ የሚተጋ
ለኸቲማው የሚሰጋ
በቀደር ያመነ
በአደጋ የሰከነ
የኔ ብቻ የማይል
ድክመቱን የሚቀበል
ታላቁን አክባሪ
ለታናሹ ራሪ
ፈርዱን ቸል ያላለ
ከሱናውም ያለ
ንግግሩ ተግባር
ህይወቱ ቁምነገር
ለእምነቱ ሰሪ
ለዲኑ ተቆርቇሪ
እውቀትን ፈላጊ
ለበጏ ሁሉ ጓጊ
በኑሮው የረጋ
ባለው የተብቃቃ
ስሜቱን የገታ
ነፍስያውን የረታ
ጏደኞቹ ጥሩ
አሏህን የሚፈሩ
መሞቱን ያወቀ
ቀድሞ የሰነቀ
ውሎው ያማረለት
ኸይር የጨመረበት
ለጊዜው የሚሳሳ
ስንፍናን የረሳ
ንዴቱን የያዘ
ለኢብሊስ ያልታዘዘ
የወጣቱ ተልዕኮ አድራሻ
ኢስላማዊ መጽሐፎችን ያውርዱ |
---|